በውሉ ባለቤት ሞት ጊዜ ብቻ ለቤተሰብ የሚጠቅም ዋስትና ሲሆን የቤተሰብ ገቢ ምንጭ የሆኑት ግለሰብ ሲሞቱ፣ ቤተሰባቸው በችግር ላይ እንዳይወድቁ የ‹‹ተርም›› መድን ትክክለኛ መፍትሔ ነው፡፡
የተርም መድን በጣም ዝቅተኛ በሆነ የአረቦን ክፍያ ከፍተኛ የሕይወት ዋስትና ሽፋን የሚያስገኝ ነው፡፡
የተርም ዋሰትና ጥቅም በዚህ ብቻ አያበቃም፡፡ ለምሳሌ አንድ ሰው ቤት ለመስራራት ከባንክ ብድር ወስደው ወይም ዕቁብ ተቀብለው ሳይከፍሉ ቢሞቱ ‹‹ተርም›› ዋስትና ካላቸው ውሉን የሰጠው የኢትዮጵያ መድን ድርጅት ዕዳቸውን ይከፍላል፡፡ ቤትና ንብረት ከመሸጥና የቤተሰብ ኑሮ ከመቃወስ ይድናል፡፡ በዋስ ላይ የሚደርስ መጉላላትም ይቀራል፡፡ |